Notice: Undefined index: title in /home/hawassao/public_html/subpage_articles.php on line 174

Notice: Undefined index: title in /home/hawassao/public_html/subpage_articles.php on line 176

Notice: Undefined index: title in /home/hawassao/public_html/subpage_articles.php on line 216

Notice: Undefined index: title in /home/hawassao/public_html/subpage_articles.php on line 218

ሻምበል አበበ ቢቂላ አጭር የህይወት ታሪክ

 

ሻምበል አበበ ቢቂላ (Abebe Bikila)

 

 

ሻምበል አበበ ቢቂላ በደብርሃን ከተማ በደነባ ልዩ ስሟ ጃቶ የምትባል ቦታ ከአባቱ አቶ ቢቂላ ደምሴ እን ከእናቱ ወ/ሮ ውድነሽ መንበሩ ነሐሴ 30 ቀን 1925 ዓ.ም. ተወለደ:: አበበ የቄስ ትምህርት እንደተማረና ከልጅነቱ ጀምሮ የገና ጨዋታ ጎበዝ እንደነበረ ይነገራል:: በመሆኑም ወደ አዲስ አበባ በመሄድ በክብር ዘበኛ በወታደርነት ተቀጠረ::

የ1948ቱ የሜልቦርን ኦሎምፒክ ኢትዮጵያን ወክለው የተሳተፉት አትሌቶች የለበሱት ዩኒፎርም እና አገራቸውን ወክለው መሮጣቸው የፈጠረበት መነሳሳት በሀገር ውስጥ የሚደረጉ የ5ሺ እና 10ሺ ሜትር ውድድሮች ላይ መካፈል ጀመረ:: በወቅቱ በጀግናው ዋሚ ቢራቱ ተይዞ የነበረውን ክብረ ወሰን በማሻሻል እውቅናን አገኘ:

 

ለ1952 ዓም የሮም ኦሎምፒክ እንዲሳተፍ ከሲውድናዊ አሰልጣኙ ኦኒ ኒስካነን ጋር በጫማም በባዶ እብሩም መለመዳዱን እና በጊዜው በጫማ በሚለማመድበት ሰዓት የተወሰነ ይዘገይ እንደነበረ ይነገራል:: በመሆኑም በባዶ እግሩ ተወዳድሮ ክብረ ወሰን በማሻሻል እና በማሸነፍ የመጀመሪያው  የጥቁር ታላቅ አትሌት ሆነ::  በዚህም ድል የተነሳ የጣልያን ጋዜጠኞች“ኢትዮጵያን ለመውረር የጣልይን አገር ወታደር ሁሉ አስፈልጎ ነበር ኢትዮጵያ ግን አንድ ወታደር ብቻ ልካ ድፍን ሮምንወረረችው” ሲሉም ዘግበው ነበር:: በዚህም የተነሳ Bikila የሚል ከጋዶ እግር ጋር የሚመሳሰል ጫማ ተሰርቶ በአገልግሎት ላይ ይገኛል::

 

ከዚህ ድል መልስ የከሸፈው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ጋር በተያያዘ አበበ ተጠርጥሮ ለተወሰነ ግዜ ታስሮም ነገር:: ሁለተኛ የኦሎምፒክ ወርቁንም 1957 ዓ.ም. በቶክዮ አሸንፉአል:: ከዚህም በተጨማሪ በብዙ የአለማቀፍ የማራቶን ውድድር በአንደኛነት ማጠናቀቁ ይገለጻል::  

 

አበበ ከወ/ሮ የውብዳር ወ/ጊዮርጊስ ጋር በትዳር 4 ልጆችን ያፈሩ ሲሆን 1961 ዓ.ም. በተሽለማት መኪና በመንቀሳወስ ላይ እንዳለ አደጋ ደርሶበት ለ5 ዓመታት ከወገቡ በታች ሽባ ሆኖ 1966 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም ተለይቷል::

ምንጭ፡-ሰዋሰዉ