Tenders

 

Type: Construction

 

Organization: የሲዳማ ዞን የጎርቼ ወረዳ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት

Dead Line: 2016-04-06

 

Tender Detail:

 



የሲዳማ ዞን የጎርቼ ወረዳ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት
በጎርቼ ከተማ 3 እና በሀሮሽፋ ከተማ 2 በድምሩ 5 ኮንቴነር ለማስገባት ህጋዊ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡

በዚሁ መሰረት፡-

  1. ደረጃቸው GC/BC 9 እና ከዚያ በላይ ሆነው ህጋዊ ፈቃድ ያላቸው፣

  2. የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና የ2008 ዓ.ም ግብር የከፈለበትን መረጃ ማቅረብ የሚችል፣

  3. በግንባታ ሂደት ችግር ምክንያት ማስጠንቀቂያ ያልተሰጠውና የጥሩ አፈፃፀም ሰርተፊኬት ያለው፣

  4. የጨረታው ማስከበሪያ (Bid Bond) ከሚያቀርበው የጠቅላላ ዋጋ 2 በባንኩ በተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ (CPO) የየባንክ ጋራንት ማስያዝ የሚችል፣

  5. ተጫራቾች የጨረታ ዶክመንቱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን አንስቶ በ7 ተከታታይ የስራ ቀናት የማመለስ 100.00 /አንድ መቶ ብር/ በጎርቼ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ከፍለው ገንዘቡ የተከፈለበትን ደረሰኝ በማቅረብ ከጎርቼ ወረዳ ፋ/ኢ/ል/ጽ/ቤት መ/ፋ/አስ/ስራ/ሂደተ የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላሉ፣

  6. ለጨረታው ሰነድ በተጫራቾች መመሪያ መሰረት ተሞልቶ ኦርጅናልና 2 ፎቶ ኮፒዎች ለየብቻቸው በሰም ታሽጎ ሁሉም ዶክመንት በአንድ ትልቅ ፖስታ ውስጥ ተከተውና በሁሉም ዶክመንት ላይ ህጋዊ የሆነ ማህተም በመምታት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት በ8ኛ የስራ ቀን ከጠዋቱ 5፡00 እስከ 6፡30 ሰዓት በጎርቼ ወረዳ ፋ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ለዚሁ አገልግሎት በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፣

  7. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት /ባልተገኙበት/ ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ቦታ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ይከፈታል፣

  8. የወቅቱን የገቤ ዋጋ ያላገናዘበ ጨረታ ተቀባይነት አይኖረውም ከቀረበው የዋጋ ትንታኔ መያያዝ አለበት፣

  9. አሸናፊው ተጫራች ከባንክ /ከአደራጁ መ/ቤተ ከኦሞ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ዋስትና ማቅረብ ይኖርበታል፣

  10. አሰሪው መ/ቤት የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ማሳሰቢያ፡- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በስራ ቀን ላይ ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይሆናል፡፡

 

በሲዳማ ዞን የጎርቼ ወረዳ ፋ/ኢ/ል/ጽ/ቤት