Catagory Lists
Tenders
Type: Multiple Items
Organization: የፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን
Dead Line: 2016-06-01
Tender Detail:
የፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ጀነሬተር 500KVA፣ የሰራተኞች ሰዓት መቆጣጠሪያ ማሽን፣ የብር መቁጠሪያ ማሽን እና ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾች፡-
- በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣
- በግዢ ኤጀንሲው ድረ ገጽ ላይ በአቅራቢዎች ሊስት ውስጥ የተመዘገቡ፣
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑና በጨረታ ለመሳተፍ የድጋፍ ደብዳቤ ያላቸው፣
- የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ከባለስልጣን መ/ቤት ቢሮ ቁጥር 304 መግዛት ይችላሉ፣
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ 10,000.00 /አስር ሺ ብር/ በባንክ በተመሰከረለት ቼክ ወይም ሲፒኦ በትራንስፖርት ባለስልጣን ስም አሰርተው ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፣
- ማንኛውም ተጫራች በሌሎች ዋጋ ላይ ተንተርሶ የሚያቀርበው ዋጋ ተቀባይነት የለውም፡፡
- የጨረታው መዝጊያና መክፈቻ ቀን በ23/9/2008 ዓ.ም በ4፡00 ሰዓት የጨረታ ሰነድ ማስገቢያ ሳጥን ታሽጎ በ4፡30 ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋና የቴክኒክ መግለጫ እና የዋጋ ማቅረቢያ ፕሮፖዛል ሰነድ ዋናውንና ቅጂውን/ኮፒ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ አድርገው ለዚሁ አገልግሎት በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፣
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0115 51 02 44 የውስጥ መስመር 231 መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን