Tenders

 

Type: Construction

 

Organization: የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ከተማ ልማት ቤቶችና ኮንስትራክሽን አገልግሎት ጽ/ቤት

Dead Line: 2016-06-05

 

Tender Detail:

 





የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ከተማ ልማት ቤቶችና ኮንስትራክሽን አገልግሎት ጽ/ቤት በደብረብርሃን ከተማ ዋናው አስፋል መንገድ ላይ 7 ኪ/ሜ የመንገድ ላይ መብራት ዝርጋታ ለማሰራት በኤሌክትሮሜካኒካል  (Electromechanical) ደረጃ 4 እና በላይ የሆኑ በዘርፉ የ2008 ዓ.ም የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ፣ የታደሰ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT)  ተመዝጋቢ የሆኑ እና የግብር ከፋይነት መለያ (TIN) ያላቸው ስራ ተቋራጮች እንዲወዳደሩ ይጋብዛል፡፡

  1. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ከተማ ልማት ቤቶችና ኮንስትራክሽን አገልግሎት ጽ/ቤት ግዥና ፋይናንስ ስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 23 በመምጣት የማይመለስ ብር 500 በመክፈል ዘወትር በስራ ሰዓት ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ መግዛት ይችላሉ፡፡
  2. የስራውን ዝርዝር፣ ቴክኒካል መገምገሚያ መስፈርቶች እና የሚያስፈልጉ ሌሎች መረጃዎችን በጨረታ ሰነዱ ላይ ይገኛሉ፡፡
  3. የቴክኒካል መወዳደሪያ ሰነዱ ኦሪጅናል እና ከሁለተ ኮፒ ጋር የድርጅቱ ህጋዊ ተወካይ ፊርማ እና ማህተም በየገጹ ተደርጎበት ኦሪጅናልና ኮፒ በማለት ለየብቻው መቅረብ አለበት፡፡
  4. የፋይናንሻል መወዳደሪያ ሰነዱ ኦሪጅናል እና ከሁለት ኮፒ ጋር የድርጅቱ ህጋዊ ተወካይ ፊርማ እና ማህተም በየገጹ ተደርጎበት ኦሪጅናልና ኮፒ በማለት ለየብቻው መቅረብ አለበት፡፡
  5. የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 100,000.00 /አንድ መቶ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (CPO) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (Unconditional Bank guarantee) በስማቸው በጽ/ቤታችን አድራሻ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  6. ተጫራቾች የቴክኒካልና ፋይናንሻል መወዳደሪያ ሰነዳቸውን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ከተማ ልማ ቤቶችና ኮንስትራክሽን አገልግሎት ጽ/ቤት ግዥና ፋይናንስ ደጋፊ ስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 29 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ማስታወቂያው በግልፅ ከወጣበት እለት ጀምሮ በ21 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው በ22ኛው ቀን ሰኔ 3/2008 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች በራሳቸው ምክንያት ባይገኙ የጨረታ ሰነዱ ተሟልቶ ከተገኘ ጨረታው ይከፈታል፡፡
  7. ዘግይቶ የቀረበ የመጫረቻ ፖስታ ተቀባይነት የለውም፡፡
  8. የቴክኒካል ግምገማ ውጤት እና የፋይናንሻል ግምገማ የሚደረግበት /የሚከፈትበት/ ቀን በውስጥ ማስታወቂያ ይገለጻል፡፡
  9. መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ወይም አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብት አለው፡፡
  10. በማስታወቂያው ላይ ያልተገለጹ ነገሮች ቢኖሩ በአብክመ የግዥ አፈፃፀም መመሪያ መሰረት እና በተዘጋጀው የጨረታ ሰነድ መሰረት ተፈጻሚ ይሆናል፡፡ ተጫራቾች ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በስቁ 011 681 2857/2717 ከሰኞ እስከ አርብ ባሉት የስራ ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት በመደወል መጠየቅ ይችላሉሉ፡

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜን ሸዋ ዞን የደብረበርሃን ከተማ አስተዳደር ከተማ ልማት ቤቶችና ኮንስትራክሽን አገልግሎት ጽ/ቤት ግዥ ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ደጋፊ የስራ ሂደት