Catagory Lists
Tenders
Type: Construction
Organization: የዳሞቱ ፑላሳ ወረዳ ፋ/ኢኮ/ል/ጽ/ቤት
Dead Line: 2016-06-04
Tender Detail:
በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክ/መ በወላይታ ዞን ዳሞት ፑላሳ ወረዳ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት ለወረዳው ውሃ ማዕድን ኢነርጂ ልማት ጽ/ቤት የሻንቶ ከተማ ውስጥ ውሃ መስመር ዝርጋታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የሚችሉ የስራ ተቋራጭ
- በመሰረተ ልማት ሚኒስቴር ተመዝግበው የ2008 ዓ.ም ግብር በመክፈል ፈቃዳቸውን ያሳደሱና ተ.እ.ታ (VAT) ተመዝጋቢ የሆኑ፣ የቲን ተመዝጋቢ የሆነ፣ በዘርፉ የታደሰ የንግድ ስራ ፈቀድና የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፡፡
- ደረጃቸው WC/WWC 7 እና ከዚያ በላይ በውሃ ስራዎች ግንባታ ፈቃድ ያላቸውና መልካም የስራ አፈፃፀም ከሥራው ጋር ተያያዥነት ያለውን የሥራ አፈፃፀም ማቅረብ የሚችሉ
- ተጫራቾች ዝርዝር የጨረታውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት ለዶክመንት የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ በመክፈል ከዳሞት ፑላሳ ፋይ/ኢኮ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 09 መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ከሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ ብር 2% /ሁለት ፐርሰንት/ ጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተመሰከረለት ቼክ (CPO) ከጨረታው ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ ኦርጅናልና 2(ሁለት) የኦርጅናሉን ፎቶ ኮፒ ለየብቻው በታሸገው ኤንቨሎፕ ሙሉ አድራሻቸውንና የፕሮጀክቱን ስም በመጥቀስ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ መክተት ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታው ሳጥን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት በ15 ተከታታይ ቀናት ቀጥሎ በሚውለው የሥራ ቀን 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዕለቱ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 4፡30 ሰዓት በዳ/ፑ/ወ/ፋ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 09 ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች በሚያቀርቡበት በነጠላ ዋጋ የማይነበቡና ስርዝ ድልዝ ያለው መሆን የለበትም፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ በስ.ቁ 0461191219 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ
የዳሞቱ ፑላሳ ወረዳ ፋ/ኢኮ/ል/ጽ/ቤት