Tenders

 

Type: Building Materials

 

Organization: የአማራ ውሃ ስራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት

Dead Line: 2016-06-11

 

Tender Detail:

 





ድርጅታችን ከዚህ በታች በሰንጠረዥ የተገለፁትን የተለያዩ ቧንቧዎች ድርጅታችን ድረስ በማቅረብ የሚሸጡ አቅራቢ ድርጅቶችን በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡


ተ.ቁ

የእቃው ዓይነት

መለኪያ

ብዛት

ሎት 1

DCO pipe

በቁጥር

4,500

ሎት 2

GS pipe

በቁጥር

17,500

 

ስለዚህ ከዚህ በታች የተገለፁትን የጨረታ መወዳደሪያ መስፈርቶችን የሚያሟላ ማንኛውም አቅራቢ ድርጅት በጨረታው መወዳደር ይችላል፡፡

  1. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የተ.እ.ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑና የግብር ከፋይነት ምዝገባ ሰርተፍኬት ቁጥር እና የምዝገባ የምስክር ወረቀት ያላቸው መሆን አለበት፡፡

  2. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚውል የተ.እ.ታክስን ጨምሮ ለሚያቀርቡት ዋጋ 1%  (አንድ) ማስያዝ አለባቸው::

  3. መ/ቤቱ አሸናፊውን ተጫራች ድርጅት በሚመርጥበት ጊዜ የሚገዛውን የእቃ መጠን እንዳስፈላጊነቱ እስከ 25% ሊቀንስ ወይም ሊጨምር ይችላል፡፡

  4. ተጫራቾች ከላይ በሰንጠረዥ ለተገለፁት ቧንቧዎች የሚያቀርቡበት ዋጋ እና ኦርጅናል ቴክኒካል ስፔስፊኬሽን ከሚያሳይ ብሮሸር ጋር ማቅረብ አለባቸው፡፡

  5. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ማለትም የቴክኒክና የዋጋ ሰነዳቸውን ለየብቻ ሆኖ በአንድ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ እስከ ሰኔ 3 ቀን 2008 ዓ.ም ውስጥ የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ባህር ዳር ከተማ ከሚገኘው ዋና መ/ቤታችን አማራ ውሃ ስራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት ዋናው መ/ቤት የተባበሩት ማደያ ፊት ለፊት አረጋውያን ህንፃ ቢሮ ቁጥር 23 በመቅረብ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡

  6. ጨረታው ሰኔ 3 ቀን 2008 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን 9፡30 ሰዓት ይከፈታል፡፡

  7. በጨረታው ለተገለፁት እቃዎች ዝርዝር የጨረታ ሰነድ ከድርጅታችን ድረ ገጽ() ላይ ማግኘት ይችላሉ፡፡

  8. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

  9. ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 058 222 17 51 መደወል ይችላሉ፡፡

ፖ.ሣ.ቁ 106

ስልክ ቁጥር 058 220 45 27

Fax  058 226 60 11

ባህር ዳር

የአማራ ውሃ ስራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት