Tenders

 

Type: Construction

 

Organization: የደ/ወርቅ ከተማ መሪ ማ/ቤት

Dead Line: 2016-06-10

 

Tender Detail:

 

 

 

 

በአብክመ በመስራቅ ጎጃም ዞን በእና/እና/ወረዳ የደ/ወርቅ ከተማ መሪ ማ/ቤት የግዥ ፋ/ን/አስ/ደ/የሥራ ሂደት በጥንቃቅን ለተደራጁ ሥራ አጥ ወጣቶች ለመስሪያ የሚሆን የሼድ ግንባታ ለማስገንባት ስለፈለግን ደረጃ GC/BC 10 እና ከዚያ በላይ ለሆኑ ሕጋዊ ፈቃድ ያላቸው እና የመልካም ሥራ አፈፃፀም ማቅረብ የሚችሉ የሥራ ተቋራጭ ለማጫረት ይፈልጋል፡፡

 

  1. የዘመኑን የታደሰ ሕጋዊ ፈቃድ ያላቸው፡፡

  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡

  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (tin) ያላቸው እና የወቅቱን የገበያ ዋጋ ማቅረብ የሚችሉ፡፡

  4. ከ50,000 (ሀምሳ ሺ ብር) በላይ ለሚገመቱ የጨረታ ሰነዶች የቫት ተመዝጋቢነት ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፡፡

  5. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ሲመጡ ከላይ ከተራ ቁጥር ከ1-4 የተጠቀሱት እና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዞ ማቅረብ አለባቸው፡፡

  6. ተጫራቾች ሰነዱን ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት የማይመለስ ብር 50 /ሀምሳ ብር/ በመክፈል ሰነዱን ከዥ ፋ/ን/አስ/ደ/የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 1 ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

  7. የጨረታው ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦነድ/ ከጠቅላላ ዋጋ 1% በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ ከተረጋገጠ ሲፒኦ ከጨረታው መዝጊያ በፊት ገቢ ማድረግ ይኖርበታል፡፡

  8. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ላይ በእያንዳንዱ ገጽ ላይ ማህተማቸውን እና ፊርማቸው የግንባታውን ኮፒ እና ኦርጅናሉን በማያያዝ በሰም በታሸገ ፖስታ በማሸግ ሰነዱን በማስገባት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ቢሮ ቁጥር 1 ማስገባት ይኖርበታል፡፡

  9. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ጊዜ ለ21 ተከታታይ ቀናት ይቆይና በ11፡30 ሰዓት ተዘግቶ በ22ኛው ቀን በ4፡00 ይከፈታል፡፡

  10. በ22ኛው ቀን የበዓላተ ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በ4፡00 ሰዓት ይከፈታል፡፡

  11. አሸናፊው ተጫራች አሸናፊነቱ ከተገለፀበት በ5 ቀናት ውስጥ የውል ስምምነት በመያዝ የአሸነፈበትን የዕቃ ግንባታውን /የአገልግሎቱን/ ጠቅላላ ዋጋ 10 የግዥ ውል ማስከበሪያ ዋስትና በጥሬ ገንዘብ /በባንክ በተረጋገጠ የባንክ ሲፒኦ ማስያዝ ይኖርበታል፡፡

  12. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

  13. በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ በጨረታው ዝርዝር መረጃ ቢሮ ቁጥር 1 በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 0586630004 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

በአብክመ በምስራቅ ጎጃም ዞን በእና/እና ውጋ ወረዳ

የደ/ወርቅ ከተማ መሪ ማ/ቤት