Tenders

 

Type: Electronics

 

Organization: የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋናው መ/ቤት

Dead Line: 2016-06-18

 

Tender Detail:

 




  1. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የምዕራብ አዲስ አበባ ሪጅን ዋየር ቢዝነስ ታየር -1 ለተለያዩ የኦፕሬሽን እና ለአዳዲስ የመስመር መዘርጋት ስራዎች የሚያገለግሉ የጭነት መኪና፣ ደብል ጋቢና ፒካፕ እና ከሬኖችን በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡

 

ተ.ቁ

የተሽከርካሪው ዓይነት

የሚፈለገው የተሽከርካሪ ብዛተ 

የመዝጊያ ቀን እና ሰዓት

የመክፈቻ ቀን እና ሰዓት

ሎት 1

5 ቶን እና ከዚያ በላይ የመጫን/የመሸከም ጉልበት ያላቸው ተሽከርካሪዎች

10

ሰኔ 14 ቀን 2008 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00

ሰኔ 14 ቀን 2008 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30

ፒክ አፕ ደብል ጋቢና

10

ሎት 2

ከ6ቶን እና ከዚያ በላይ ክብደት ማንሳት የሚችሉ እና 12ሜ እና ከዛ በላይ ከፍታ ማንሳት የሚችሉ ክሬኖች

3

 

  1. ተጫራቾች የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ ዓመታዊ የቴክኒክ ምርመራ ያከናወኑበትን እና የተሽከርካሪዎቹን የኢንሹራንስ ዋስትና ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው፡፡

  2. በድርጅቱ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ከዚህ በታች ከተጠቀሰው አድራሻ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ማግኘት ይቻላል፡፡

በኢተዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

የም/ዕ/አ/ሪጅን ፕሮክዩርመንት ሎጄስቲክስና ዌርሃውሲንግ ቢሮ፡፡

ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1233

የስልክ ቁጥር 011 557 29 34

ሜክሲኮ አደባባይ 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 08 አዲስ አበባ

  1. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ለእያንዳንዱ ሎት ብር 20,000 /ሃያ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዝ አለባቸው፡፡

  2. ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን ሰነድ በሰም በታሸገ ፖስታ በማድረግ ጨረታ ቁጥር ኢኤአ 002/2008 የሚል ምልክት በማድረግ እስከ ሰኔ 14 ቀን 2008 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓተ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በምዕ/አ/አ/ሪጅን ፕሮክዩርመንት ሎጄስቲክስና ዌርሃውሲንግ ቢሮ ቁጥር 08 ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡

  3. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ሰኔ 14 ቀን 2008 ዓ.ም ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ በ8፡30 ሰዓት ይከፈታል፡፡ የመክፈቻው ቀን ብሄራዊ በዓል ወይም ቅዳሜ እና እሁድ ከሆነ በሚቀጥለው ቀንና ሰዓት ይከፈታል፡፡

  4. ኢንተርፕራይዙ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋናው መ/ቤት