Catagory Lists
Tenders
Type: Cleaning Service
Organization: የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት
Dead Line: 2016-06-19
Tender Detail:
የደ/ማ/ከ/አስ/ገ/አካ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ለከተማ አስ/ሴ/መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል የጽ/መሳሪያና የጽዳት እቃዎችን ከአቅራቢ ድርጅቶች በሎት ጠቅላላ ዋጋ ድምር አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ፡-
- የዘመኑን የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸው፡፡
- የግዥ መጠን ብር 50,000.00 /ሀምሣ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግት የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የሚገዙ እቃዎችን አይነት ዝርዝር መግለጫ፣ /ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 20 /ሃያ ብር/ ብቻ በመክፈል ከገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ክፍል ቢሮ ቁጥር 5 ማግኘት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ለሚወዳደሩበት የእቃው ጠቅላላ ዋጋ 1% በባንክ በተመሰከረ የክፍያ ትእዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በትሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን ሞልተው በታሸገ ፖስታ በማድረግና ግዥና ፋይ/ንብ/አስ/የስ/ሂደት ቢሮ ቁጥር 5 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው በ16ኛው ቀን ፍላጎት ባላቸው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ታሽጎ በ4፡00 ሰዓት ይከፈታል፡፡
- አሸናፊው ድርጅት እቃውን ደ/ማ/ከተማ አስ/ገን/ኢኮ/ል/ጽ/ቤት/ን/ክፍል ይዞ በመምጣት ማስረከብ አለበት፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ፡- ስልክ ቁጥር 058 771 3362
የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት