Catagory Lists
Tenders
Type: Construction
Organization: የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተር ፕራይዝ
Dead Line: 2016-08-15
Tender Detail:
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተር ፕራይዝ ለደብረዘይት ኢንጂነሪንግ ኮሌጅ ግንባታ ፕሮጀክት አገልግሎት የሚውል supply, insall, test and commission audio system ግዥ ለመፈፀም ተጫራቾችን በግልፅ ጨረታ ለማወዳደር ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም፡-
- ተጫራቾች በመስኩ የተሰማሩ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሚያቀርቡ ገንዘብ በተጫራቾች መመሪያ ተራ ቁጥር 7.3 እና 7.4 በተጠቀሰው መሰረት መሆን አለበት፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ዘወትር በስራ ሰዓት ወሎ ሠፈር አካባቢ በሚገኘው የመከላከያ ኮንስትራክሽን ዋናው መ/ቤት የግዥ የሥራ ሂደት ኬዝ ቲም ቢሮ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸው ዕቃዎች ካታሎግ፣ የጥራት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት (Quality certificate) በካታሎጉ ላይ የሚወዳደሩበትን ዕቃ ለይቶ በማመልከት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቧቸው ዕቃዎች በተጠቀሰው ብዛት (Quantity) መሠረት መሆን ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ እስከ ነሐሴ 8 ቀን 2008 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ነሐሴ 8 ቀን 2008 ዓ.ም ከቀኑ 8፡15 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
- ኢንተርፕራይዙ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ፡- የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ
የቀጥታ ስልክ ቁጥር 0114 40 34 33/34
ማዞሪያ 0114 42 22 70/71/72
ፖ.ሳ.ቁ 3414
ፋክስ፡- 0114 40 04 71/0114 42 07 46