Tenders

 

Type: Stationery

 

Organization: በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት

Dead Line: 2016-09-26

 

Tender Detail:

 




በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በ2009 በጀት ዓመት አንደኛ ዙር ግዥ የሚያስፈልገውን ሎት አንድ የህትመት ስራ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

በዚሁ መሰረት በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልግና የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟላ ማንኛውም ህጋዊ ተጫራቾች በጨረታው መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ባዘጋጀው የዕቃና አገልግሎት አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ፡፡
  2. ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የሚያረጋግጥ በግብር አስገቢው ባለስልጣን የተሰጠ ማስረጃ ማቅረብ፡፡
  3. ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት፡፡
  4. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 የስራ ቀናት ውስጥ የማይመለስ ብር 50 /ሀምሳ ብር/ በመክፈል የጨረታውን ሰነድ በስራ ሰዓት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ንጉሴ ትሩፌ ህንጻ 5ኛ ፎቅ ግዥና ፋይናንስ አስተዳደር ቡድን ላይ ቢሮ በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ፡፡
  5. ተጫራቾች በገዙት ሰነድ መሰረት ዋናውንና ኮፒውን የሚወዳደሩበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አስራ አምስት /15/ ተከታታይ ቀናት በተጠቀሰው ቢሮ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የጠቅላላውን ዋጋ 2% በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በሚል ስም በማዘጋጀት በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም ሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  7. ጨረታው መስከረም 20 ቀን 2009 ዓ.ም ከሰዓት 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዕለቱ ወይም መስከረም 20 ቀን 2009 ዓ.ም ከሰዓት 8፡30 ሰዓት ይከፈታል፡፡
  8. ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለተጨማሪ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0112 73 25 91 /0112 73 20 02/0118 69 92 12 በመደወል መረጃ ማግኘት ይቻላል፡፡

አድራሻ፡- ከመሳለሚያ ወደ ታይዋን በሚወስደው መንገድ ንጉሴ ቱሩፌ ህንፃ 5ኛ ፎቅ ግዥና ፋይናንስ አስተዳደር ቢሮ፡፡

በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት