Tenders

 

Type: Autos

 

Organization: የደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ፍትህ ቢሮ

Dead Line: 2016-03-05

 

Tender Detail:

 

የደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ፍትህ ቢሮ የሚገለገልባቸው መኪናዎች የአንድ ዓመት የሚቆይ በኮንትራት ማስጠገን ይፈልጋል፡፡
በዚህ መሠረት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ድርጅቶች በጨረታው እንድትሣተፉ ይጋብዛል፡፡

        1. በዘርፋ የታደሰ ህጋዊ ፋቃድ ያላቸውና የዘመኑ ግብር ለመክፈላቸው መረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡

        2. የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN number) ሠርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ፡፡

        3. ከትራንስፖርት ቢሮ ወይም ከክልሉ ትራንስፖርት ቢሮ የደረጃ 3 ወይም ከዚያ በላይ የብቃት ማረጋገጫ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፡፡

        4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የተጨማሪ እሴት ታክስ ጨምሮ በሚያቀርብ ዋጋ ላይ 2% በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ(CPO)ጨረታው በመክፈቱ በፊት ማስያዝ አለባቸው፡፡

        5. ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ከመሥሪያ ቤቱ ግዥና ፋይ/ን/አስ/ደ/የሥራ ሂደት በግንባር ቀርበው ወይም በህጋዊ ወኪል አማካኝነት የማይመለስ ብር 50/ሃምሳ ብር/መውሰድ ይችላሉ፡፡

        6. ተጫራቾች ለእያንዳንዱ የጥገና አገልግሎት በሚያቀርቡት ዋጋ ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ(VAT) በመጨመር የቴክኒክና ፋይናንሻል ሰነድ ኦርጅናል ሁለት ኮፒ በተለያዩ ፖስታ/ኤንቨሎፕ/በማሸግ ዘውትር በሥራ ሰዓት ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ተከታታይ ቀን 4፡00 ሰዓት ድረስ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ፋትህ ቢሮ ግዥና ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 14 በመቅረብ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡

        7. የጨረታ ሳጥን በዚሁ ዕለት/16ኛው ቀን/ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ይታሸግና በ4፡05 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡16ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን ከላይ በተገለጸው ቀን ይከፈታል፡፡

        8. ተጫራቾች በቂና ምቹ የጥገና አገልግሎት መስጫ ቦታ ያላቸው በሆኑን ለጨረታው ኮሚቴ ማሳየት ይኖርባቸዋል፡፡

        9. አሠሪው መ/ቤት አገልግሎት ማግኘት የሚፈለገው በሃዋሳ ከተማ ነው፡፡

        10. ጨረታው ውስጥ እስከሚገለጽ ጊዜ ድረስ የፀና ይሆናል፡፡

        11. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 0462207327 ደውለው ይጠይቁ፡፡