Tenders

 

Type: Multiple Items

 

Organization: ማርኮን ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር

Dead Line: 2017-02-06

 

Tender Detail:

 






ማርኮን ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበርገለገሉ ተሽከርካሪዎች ማሽነሪዎች፤የድንጋይ ወፍጮ፤ቫይሬተሮች፤ኮምፕረሰር፤ ኮምፓክተሮች የቢሮ ማሽነሪዎች፤የቢሮ ዕቃዎች ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ የወጣ ማስታወቂያ ማገርኮን ኃ/የተ/የግል ማህበር ያገለገሉና በጥሩ ሁኔታ ላይ የሚገኙ ተሽከርካሪዎች፤ የድንጋይ ወፍጮ፤ቫይብሬተሮች፤ኮምፓክተሮች፤ኮምፕረሰር ልዩ ልዩ ያገለገሉ የቢሮ ዕቃዎችና ውድቅዳቂ ብረቶችና ፓኔሎችን እንዲሁም ሌሎችንም ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል::

 

ስለሆነም፡-

1. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራቾች የጨረታው ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ከ2ኛ ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት የማይመለስ ብር 50(ሀምሳ ብር) በመ/ቤቱ ገንዘብ ቤት በመክፈል የጨረታውን ሰነድ ማግኝት ይቻላል::

2. ተሽከርካሪዎችንና ማሽነሪዎችን የጨረታ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ አቃቂ ቃሊቲ ሳሪቲ በሚገኝው የመስሪያ ቤቱ ዋና መጋዘን ዘወትር በስራ ሰዓት በአካል ቀርበው መመልከት ይችላሉ::

3. ተጫራቾች ከሚያቀርቡት ዋጋ 5% የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር በማያያዝ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ እስከ ጥር 29 ቀን 2009 ዓ.ም ከቀኑ 3 ሰዓት ድረስ ገንዘብ ቤት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው::

4.ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት በመሰብሰቢያ አዳራሽ ጥር 29 ቀን 2009 ዓ.ም ከቀኑ በ 8 ሰዓት ይከፈታል

5. በቂ የዋስትና ማስከበሪያ በ(CPO) ወይም በካሸ ያላስገቡ ተጫራቾች ከጨረታው ይሰረዛሉ::

6. የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያው ለአሸናፊዎች ከሚከፍሉት ዋጋ የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊዎች የጨረታው ውጤት እንደታወቀ በ 10 ቀናት ውስጥ ያስያዙት የጨረታ ዋስትና (CPO) ይመለስላቸዋል::

7. መስሪያ ቤቱ ለጨረታው የተሻለ መንገድ ካገኝ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ለመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ መሆኑን ያሳውቃል::

የመ/ቤቱ አድራሻ፡- ከሃና ማርያም ወደ ማሰልጠኛ በሚወስደው በካዲስኮ ቀለም ፋብሪካ በስተቀኝ ከጨርቃ ጨርቅ ኢንስቲትዩት ፊት ለፊት ሲሆን የስልክ ቁጥር 0114-391604/0114-391600/0114-391606/0911 414185 ማገርኮን ኃ/የተ/የግል ማህበር አዲስ አበባ