Catagory Lists
Tenders
Type: Agricultural Products
Organization: የሐፋርሳ መሠረታዊ ሁለገብ የገበሬዎች ኀ/ሥራ/ማህበር ኃላ.የተወሰነ
Dead Line: 2016-03-04
Tender Detail:
የሐፋርሳ መሠረታዊ ሁለገብ የገበሬዎች ኀ/ሥራ/ማህበር ኃላ.የተወሰነ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ለታጠበ ቡና መፈልፈያ ኢንዱስትሪ ግንባታ አገልግሎት የሚውሉ ማሽኖችን ህጋዊ አቅራቢዎችን በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
- የእሸት ቡና ማጠብያ ማሽን environmentally friendly washed coffee machine capacity 60 qu/hr
- Electrical generator 60KW open
ስለዚህ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የጨረታ መስፈርቶችን የሚያማሉ ሕጋዊ አቅራቢዎች በጨረታው ላይ መሳተፍ ይችላሉ፡፡
- በዚሁ ስራ መስክ የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፍቃድ እና የሥራ ልምድ ያላቸው
- የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ተመዝጋቢ የሆኑ
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸውና የዘመኑን የግብር ግዴታ እንደተወጡ የሚገልጽ ክሊራንስ የሚያቀርቡ
- የሚያቀርቡትን ዕቃ ዋጋ 5 የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተመሰከረለት ቼክ (ሲፒኦ) ማስያዝ የሚችሉ
- ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ብር 100.00(አንድ መቶ ብር) በመክፈል ከይርጋጨፌ ቡና ገበሬዎች ሕብረት ሥራ ዩኒየን ኃላ.የተ መግዛት አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቡበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን እስከ 15 የሥራ ቀናት ቃሊቲ በሚገኘው ቢሮአችን ቀርበው በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባ ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው 24/06/08 ዓ.ም ቀን 2008 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከዚሁ በታች በተገለፀው በዩኒየኑ ቅ/ጽ/ቤት አድራሻ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ማህበሩ የተሸለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- በዚሁ ስራ መስክ የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፍቃድ እና የሥራ ልምድ ያላቸው
አድራሻ፡- ከቃሊቲ አደባባይ በሃና ማሪያም መስመር 200 ሜትር ገባ ብሎ(CCRDA ጀርባ)251-0114-71-70-19/18/17 E 0911-94-42-51