Catagory Lists
Tenders
Type: Machinary
Organization: በደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መንግስት ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ
Dead Line: 2017-04-18
Tender Detail:
የደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክ/መንግስት ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ 40,000 BUT-14 SEER 3.5 TON Air conditioning እና 10 KVA UPS ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
በዚሁ መሠረት፡-
- ፍቃዳቸውን በ2009 ዓ.ም ያሳደሱ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው፣ ለተጨማሪ እሴት የተመዘገቡና መለያ ቁጥር ያላቸው፣ ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡና የታክስ መለያ ቁጥር ያላቸው፣
- ተጫራቾች ለዕቃ ግዥው የተዘጋጀው ሰነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ቅዳሜና እሁድን እንዱሁም የበዓል ቀን አካቶ ለእያንዳንዱ ዶክመንት የማይመለስ ብር 50 /ሃምሳ/ በመክፈል ዘወትር በሥራ ቀናት የንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ የግዥና ፋ/ንብ/አስ/ደ/ስራ ሂደት ከቢሮ ቁጥር 103 መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን ቴክኒካል እና ፋይናንሻል አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ እያንዳንዳቸው ለየብቻ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ 16ኛው ቀን ከጠዋቱ ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ጨረታው በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 – 6፡00 ሰዓት መ/ቤቱ የግዥና ፋ/ንብ/አስ/ደ/ስራ/ሂደት ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዶክመንቱ ይታሸግና በዚያው እለት ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ተጫራቾችና ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- 16ኛው ቀን ስራ ቀን ካልሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን ይከፈታል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 046 221 46 78 ይጠይቁን
በደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መንግስት ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ