Notice: Undefined index: title in /home/hawassao/public_html/subpage_articles.php on line 174

Notice: Undefined index: title in /home/hawassao/public_html/subpage_articles.php on line 176

Notice: Undefined index: title in /home/hawassao/public_html/subpage_articles.php on line 216

Notice: Undefined index: title in /home/hawassao/public_html/subpage_articles.php on line 218

ኢትዮጵያ የወይን ጠጅ ጠማቂ ወይም አምራች አገር አልነበረችም፡፡

ወይን ጠጅ

 

Image result for ወይን ጠጅ

 

ኢትዮጵያ የወይን ጠጅ ጠማቂ ወይም አምራች አገር አልነበረችም፡፡ ስለዚህ ስሟ በወይን ጠማቂ አገሮች ካርታ ላይ አልሰፈረም ነበር፡፡ አሁን ግን በካስቴል የወይን ጠጅ አምራች ፋብሪካ አማካኝነት ከአምና ጀምሮ ስሟ በወይን ጠጅ አምራች አገሮች ካርታ ላይ ሰፍሯል፡፡

በወይን ጠጅ ምርቶቻቸው በፈረንሳይና በሰሜን አፍሪካ ታዋቂ የሆኑት ሚ/ር ካስቴል፤ በኦሮሚያ ክልል በዝዋይ ከተማ ያስገነቡት እጅግ ዘመናዊ የወይን ጠጅ ፋብሪካ ተመርቆ ወደ ገበያ ከገባ እነሆ አንድ ዓመት ሞላው። ፋብሪካው  የተመሠረተበትን የአንደኛ ዓመት የልደት በዓል ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ የመጀመሪያውን ዓመት ፌስቲቫል አዘጋጅቶ በፋብሪካው ግቢ አክብሯል፡፡

ከድርጅቱ ጋር የሚሠሩ ወይም ምርቱን ተቀብለው የሚሸጡ ሬስቶራንቶችና ሆቴሎች ተገኝተዋል፡፡ እነዚህ ደንበኞቻቸው ወይን ጠጁን መሸጥ እንጂ ወይን እንዴት እንደሚጠመቅ አያውቁም፡፡ የወይን ፍሬ ወይም ዘለላ ከየት ተነስቶ የወይን ጠጅ እንደሚሆን የአጠማመቅ ሂደቱን ማሳወቅ የፌስቲቫሉ ዓላማ መሆኑን የካስቴል ፋብሪካ የሽያጭና ማርኬቲንግ ኃላፊ ዓለምፀሐይ በቀለ ገልፀዋል፡፡

ፋብሪካው ሥራ ሲጀምር 7 ዓይነት የወይን ጠጅ ያመርት ነበር፡፡ አሁን ሁለት ዓይነት ምርት ጨምሮ ቁጥሩን ዘጠኝ አድርሷል፡፡ ደንበኞቻቸው ምርቱን መሸጥ እንጂ አንዱ ከሌላው በምን እንደሚለይ አያውቁም፡፡ ሌላው ዓላማ በዚህ አጋጣሚ ለጠጪና ተቀባይ ደንበኞቻቸው ልዩነቱን ማሳወቅ እንደሆነ ፀሐፊዋ ተናግረዋል፡፡

ወይን፣ ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚፈልግ ዝርያ ነው፡፡ የተስተካከለ ሙቀትና እርጥበት ካልተደረገለት በቀላሉ ለበሽታ ይጋለጣል፡፡ ፋብሪካው የሚጠቀመውን አራት ዓይነት ዝርያ ቦርዶ ከተባለ የፈረንሳይ ከተማ በከፍተኛ ጥንቃቄ ነው ያመጣው፡፡ “ዘሮቹን ያመጣነው፣ ተስማሚና ምቹ ሙቀትና እርጥበት ባለው ፍሪጅ ነው፡፡ ይህ ጥንቃቄ ብዙ ገንዘብ አስወጥቶናል” ብለዋል -ሃላፊዋ ዓለምፀሐይ፡፡

ወይን ጠጃቸው በመላ ኢትዮጵያ በጣም ተወዶላቸዋል፡፡ ወይን ጠጅ በዓመት ሁለት ጊዜ ማምራት ቢቻልም፣ ካስቴል ግን የሚያመርተው በዓመት አንዴ ብቻ ነው፡፡ ይህን የሚያደርገው ወይን ብዙ ጊዜ (ኤጂንግ ይባላል) በቆየ ቁጥር የጥራት ደረጃው ስለሚጨምር ነው። አምና ያመረቱት አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሺህ (1.1 ሚሊዮን) ሊትር ወይን ጠጅ በሙሉ ተሸጦ አልቋል። ለአገር ውስጥ ገበያ ካቀረቡት ውስጥ አብዛኛው (80 በመቶ ማለት ይቻላል) የተሸጠው በአዲስ አበባ ከተማ ነው፡፡ ቀጣዩን ደረጃ የያዘው ደግሞ ደቡብ ክልል መሆኑን ዓለም ፀሐይ ገልፀዋል፡፡

ለአገር ውስጥም ሆነ ለውጭ ገበያ ያቀረቡት ምርት በጣም ተወዶላቸዋል። ስለዚህ ማስፋፊያ እየሠሩ ነው፡፡ ካስቴል ወይን ጠጅ ፋብሪካ አ.ማ በሊዝ የወሰደው መሬት 497 ሄክታር ነው፡፡ የመጀመሪያው የወይን እርሻ ያረፈው በ162 ሄክታር መሬት ላይ ሲሆን ከእርሻው 1.1 ሚሊዮን ጠርሙስ ወይን ጠጅ እየተመረተ ነው፡፡ በማስፋፊያው ማምረት የተፈለገው 1.8 ሚሊዮን ጠርሙስ ወይን ስለሆነ 70 ሄክታር መሬት ላይ የወይን እርሻ ሊጨመር ነው፡፡ የቀድሞው እርሻና የፋብሪካ ግንባታ 25 ሚሊዮን ዩሮ ፈጅቷል፡፡ ማስፋፊያው የሚሠራው በ10 ሚሊዮን ዩሮ እንደሆነ ኃላፊዋ ተናግራለች፡፡

ፋብሪካው ወደ ገበያ የገባው አኬሻና ሪፍት ቫሊ የተሰኙ ሰባት ዓይነት የወይን ዝርያ ይዞ ነበር፡፡ አሁን ሁለት ጨምሯል፡፡ ከአኬሻ አራት ዓይነት ወይኖች ይመረታሉ፡፡ አኬሻ ድራይ ሬድ፣ አኬሻ ሚዲየም ሬድ ስዊት፣ አኬሻ ሚዲየም ኃይትና አኬሻ ሚዲየም ስዊት ሮዝ ወይኖች ይመረታሉ፡፡ ድራይ ሬድ ማለት ደረቅ ቀይ ወይን፣ ሚዲየም ሬድ መካከለኛ ጥፍጥና ያለው ቀይ ወይን፣ ሚዲየም ኋይት መካከለኛ ጥፍጥና ያለው ነጭ ወይን ጠጅ ሲሆን፣ ሚዲየም ስዊት ሬድ ሮዝ ለመጀመሪያ ጊዜ አሁን በኢትዮጵያ የተመረተ ሮዝ ቀለም ያለው ጣፋጭ ወይን ጠጅ ነው። ይህ ወይን ጠጅ የሚመረተው ከቀይ ወይን ሲሆን በፈርሜንተሽን (መብላላት) ሂደት ሙሉ ለሙሉ ወደ ቀይ ወይን ሳይለወጥ ሮዝ ቀለም ሲይዝ ሂደቱ ስለሚቋረጥ ሮዝ ቀለም ይኖረዋል፡፡ የሚጣፍጠው ደግሞ ስኳር ወይም ሌላ ማጣፈጫ ተጨምሮበት ሳይሆን በፈርመንቴሽን ሂደት የሚፈጠረው ስኳር ሙሉ በሙሉ ወደ አልኮልነት ሳይለወጥ የመብላላት ሂደቱ ስለሚቋረጥ መሆኑን ሃላፊዋ አስረድተዋል፡፡

ሪፍት ቫሊ ወይን ጠጅም አራት ዓይነት አለው። ሪፍት ቫሊ ካቨርኔሶ ቪኞ ሪፍት ቫሊ መርሎ፣ ሪፍት ቫሊ ሂራ የተባሉት የቀይ ወይን ጠጅ  ዓይነቶች ናቸው፡፡ ካቨርኔሶ ቪኞ ፣ መርሎና ሂራ የወይኑ ዝርያ ስም ነው። ሻዶኔ የሚባለው ወይን ደግሞ ነጭ ቀለም አለው፡፡ በአሁኑ ወቅት ገበያው የሚፈለገው ነጭ ወይን ስለሆነ ማስፋፊያ የሚደረገው የነጭ ወይን ነው ብለዋል፡፡

ለውጭ ገበያ የሚላኩት ሁለቱም ዓይነት ወይኖች አኬሻና ሪፍትቫሊ ናቸው፡፡ ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካ አገሮች የሚመርጡት አኬሻን ነው። ምክንያቱ ደግሞ ጠንካራ ስላልሆኑና ስለሚጣፍጥ ነው፡፡ ወደ አሜሪካ፣ አውስትራሊያና ቻይና የሚልኩት ሪፍት ቫሊዎቹን ነው፡፡ አሁንም ሆነ ወደፊት ትልቁ ገበያቸው ቻይናና አሜሪካ ነው፡፡ ቀዳሚውን ደረጃ የያዘው ቻይና ነው፡፡ እስካሁን ኤክስፖርት ያደረጉት የምርታቸውን 15 በመቶ እንደሆነ ኃላፊዋ ጠቅሰው፤ ከዚህ በላይ መላክ ቢፈልጉም ቀደም ሲል ኢትዮጵያ በወይን አምራች አገሮች ካርታ ውስጥ ያለመኖሯ ችግር እንደፈጠረባቸው ገልጻለች። ትልቁ ስኬታቸው የአገር ውስጥ ገበያውን ፍላጐት በመቆጣጠራቸው ቀደም ሲል ከደቡብ አፍሪካና ከሌሎች አገሮች ወይን ለማስመጣት ይወጣ የነበረውን የውጭ ምንዛሪ መቀነሳቸውን አስረድተዋል፡፡

ምርታቸው በኅብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ቢያገኝም ማትረፍ አልቻሉም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ምርት ከመጀመራቸው ቀደም ሲል የወይን እርሻውን ለአራት ዓመት ሲያለሙ ወጪያቸው በጣም ብዙ ስለነበር ለሁለት ዓመት የሚሠሩት ላለመክሰርና በዋናቸው ለመንቀሳቀስ እንደሆነ፣ ትርፍ የሚጠብቁት በሦስተኛው ዓመት መሆኑን የሽያጭና ማርኬቲንግ ማናጀሯ ገልጻለች።

ወይን የሚጠጣው ምግብ እየተበላ ስለሆነ በፌስቲቫሉ ላይ የተለያዩ አገሮች ከወይን ጋር የሚበሉ ባህላዊ ምግቦች አቅርበው ነበር፡፡ ጆን ሉካ ኢጣሊያዊ ሲሆን የአፍሪካ ወይንና አይብ የሚነግድበት ሬስቶራንት አለው፡፡ ወይን የመጠጣት ልምድ እንዳለው ጠየኩት፡፡ ኢጣሊያዊ ሆኜ እንዴት ነው ወይን የማልጠጣው? አለኝ። እንግዲያውስ ስለካስቴል ወይን ከሌሎች አገሮች ጋር እያነፃፀርክ ስለ ጥራት ደረጃው ንገረኝ ፈለኩት፡፡

አየህ! የወይንን የጥራት ደረጃ የሚወስኑ በርካታ ነገሮች አሉ፡፡ የአየሩ ሞቃት ወይም ቀዝቃዛ መሆን፣ ወይኑ የበቀለበት የአፈር ዓይነት፣ አፈሩ የያዘው ንጥረ ነገሮች ዓይነትና መጠን፣ አካባቢው፣… ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ የአፈሩ ዓይነት፣ በተለያዩ አገሮች የሚመረት ወይን ይቅርና በአንድ አገር ውስጥ በተለያየ አካባቢ የሚመረት ወይን እንዟን ማነፃፀር አይቻልም። የካስቴልን ወይን እጠጣለሁ፡፡ ከማንም ጋር ሳይወዳደር በራሱ በጣም ጥሩ ነው አለኝ፡፡ 

ምንጭ፡- አዲስ ዘመን ጋዜጣ