Notice: Undefined index: title in /home/hawassao/public_html/subpage_articles.php on line 216

Notice: Undefined index: title in /home/hawassao/public_html/subpage_articles.php on line 218

በጣና ሃይቅ ደሴቶች ውስጥ የሚገኙ ገዳማት

 

 

 

በኢትዮጵያ ትልቁ በሆነው ሃይቅ ዙሪያ በታሪክ ሃብታም የሆኑ በርካታ ገዳማት ይገኛሉ። ከእነዚህ ገዳማት አንዳንዶቹ ከ 700 አመት ዕድሜ በላይ ያላቸው ሲሆኑ በውስጣቸው ከተለያየ የሃገሪቱ ክፍሎች የተሰባሰቡ ውድ የታሪክ ቅርሶችና የመካከለኛው ዘመን የሃገሪቱ 

ነገስታትን አጽም የያዙ ናቸው።  በመሆኑም ገዳማቱ በተለያዩ ጎብኝዎችን ሲጎበኙ ይስተዋላሉ።

 
ደቅ ደሴት (Dek Island)  
ይህ ደሴት ጣና ሃይቅ ካሉት ደሴቶች ሁሉ ትልቁ ደሴት ሲሆን ከባህር ዳር ከተማ 37 ኪሜ ርቀት ላይ ይገኛል። በዚህ ደሴት ውስጥ 7 (ሰባት) አድባራትን የያዘ እና "የሰባት ደብር አገር" በመባል ይታወቃል። 
እነዚህም ደብሮች በስም ዳጋ እሥጢፋኖስ፣ ናርጋ ስላሴ፣ ቅድስት አርሴማ፣ ኮታ ማርያም፣ ዝባድ ኢየሱስ፣ ጆጋ ዮሃንስ እና ጋደና ጊዮርጊስ በመባል ይታወቃሉ።  
 
 
                ደቅ ደሴት
 
 
 
                ናርጋ ስላሴ
 
ደቅ ደሴት መጀመሪያ ለመነኮሳት ብቻ እንጂ ለአለማውያን የተከለከለ ደሴት ነበር። እየቆየ ግን ቀስ በቀስ ስዎች ወደ ደሴቱ በመምጣት፣ በመስፈር እና በመዋለድ የኗሪው ቁጥር ከፍ ሊል ችሏል። 
በአሁኑ ጊዜ የደሴቱ ነዋሪዎች የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታዮች ብቻ ናቸው። ወደ ደሴቱ የአለማውያን መግቢያ ዘመን በአራት ተከፋፍለው ይነገራሉ
1- የግራኝ አህመድ ጦርነት ጊዜ
2- እቴጌ ምንትዋብ የናርጋ ስላሴ ቤተክርስትያንን በሚያሰሩበት ጊዜ
3- በአፄ ቴዎድሮስ ዘመነ መንግስት
4- በአፄ ዮሃንስ 4ኛ ዘመነ መንግስት በነበረው የደርቡሾች ወረራ ወቅት
 
ክብራን ገብርኤል እና እንጦሥ  (Kibran Gebriel and Entoss) 
እነኝህ መንትያ ደሴቶች ከባህር ዳር ከተማ በስተ ሰሜን ምዕራብ  በጀልባ  የ45 ደቂቃ ርቀት ላይ የሚገኙ ሲሆን የደሴቶቹ መልከዐምድራዊ አቀማመጥ እና የተሸፈኑበት አረንጏዴ ደን እጅግ ውብ አድርጏቸዋል።
 ክብራን ገብርኤል ገዳም የወንድ ብቻ ገዳም ሲሆን እንጦስ ገዳም ደግሞ የሴቶች ብቻ እንደነበር ይነገራል። ይሁንና በእንጦስ ገዳም ያሉ ሴቶች በተለያዩ ምክንያት በመሰደዳቸው በገዳሟ ላይ የኢየሱስ ገዳም ገብቶ የወንዶች ብቻ ገዳም ሆኗል። 
 
 
                ክብራን ገብርኤል
 
የክብራን ገብርኤል ደሴት መጀመሪያ የተሰራው በአፄ አምደ ፅዮን ዘመነ መንግስት ሲሆን በዳግማዊ ዳዊትና ከዚያም በአዲያም ሰገድ እያሱ እንደተሰራ ይነገራል። 
ቤተክርስትያኑ በልክ በተጠረቡ ቀያይ ድንጋዮች የተሰራ ሲሆን በቤተ መቅደሱ ዙሪያ ከድንጋይ የተጠረቡ 12 አምዶች ይገኛሉ። 
በገዳሙ ውሥጥ እና በአፄ ፋሲል እንደተሰራ በሚነገርለት እቃ ቤት ከሚገኙት ዋና ዋና ታርካዊ ነገሮች መካከል የሚከተሉት ይገኙባቸዋል
 - ከቤተክርስትያኑ መቅደስ ግድግዳ ጋር ተያይዞ በተሰራ ክፍል ውስጥ የገዳሙ መስራች የአቡነ ዘዮሃንስ መቃብር
 - በሃዋርያው ሉቃስ እንደተሳለች የሚነገርላት ሰዕለ ማርያም
 - ከብረት የተሰራው የአቡነ ተክለሃይማኖት ተደራራቢ አልጋ
 - ከእንጨት የተሰሩ መቅረዝ እና አገልግል
 - መስቀሎች
 - የገበታ ላይ ሰእሎች
 - የብራና መፅሃፍት
 
ዘጌ ባህረ ገብ (Zeghe Peninsula)
የጣናን ሃይቅ ከምዕራብ ወደ ምስራቅ በመግፋት ተንሰራፍቶ የሚታየው ባህረገብ መሬት ዘጌ በመባል ይጠራል። ዘጌ ከባህር ዳር ከተማ 15 ኪሜ ርቀት ላይ የሚገኝ ነው። በዚሁ ባህረ ግብ ላይም 7 የሚሆኑ አብያተክርስትያናት ይገኛሉ። 
በስምም መሃል ዘጌ ጊዮርጊስ፣ አቡነ በትረማርያም፣ አዝዋ ማርያም፣ ውራ ኪዳነ ምህረት፣ ደብረስላሴ፣ ይጋንዳ አቡነ ተክለሃይማኖት እና  ፉሬ ማርያም በመባል ይታወቃሉ። 
 
 
                 ዘጌ ባህረ ገብ በፀሃይ ጥልቀት
 
ደብረ ማርያም (Debre Mariam)
ከባህር ዳር ከተማ በሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ በጀልባ የ20 ደቂቃ ወይም በእግር የአንድ ሰአት ተኩል እርቀት ላይ የምትገኘው ደሴት ላይ የምትገኝ
 ገዳም ስትሆን ይቺ ገዳም በአፄ አምደ ፅዮን ዘመነ መንግስት (1307 - 1337 አመተ ምህረት ) እንደተመሰረትች ይነገራል።
ገዳሟ ያለችበት አካባቢም በሁለት ተጨማሪ "ጉማሬ ባህር (በአካባቢው ብዙ ጉማሬውች ስለሚገኙ) እና "አባይ ራስ (የአባይ ወንዝ የጣና ሃይቅን ውሃ ሰንጥቆ የሚወጣበት ቦታ በመሆኑ) በሚሉ ስሞች ይታወቃል።   
 
ምንጭ 
    • የአማራ ክልል የቱሪሥት መሥህብ ያብቶች (የአማራ ቱሪዝም እና ማሥታወቂያ ቢሮ)