Tenders

 

Type: Multiple Items

 

Organization: የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

Dead Line: 2016-03-18

 

Tender Detail:

 

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

የጨረታ ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቢዝነስ ዴበሎፕመንት የሥራ ሂደት ከዚህ በታች የተጠቀሱትን ሰንደቅ ዓላማዎቸ እና የላፕቶፕ/ዶኩመንት መያዣ ቦርሳ በጨረታ አወዳድሮ አሸናፊ ከሆነ ድርጅት ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

የሰንደቅ ዓላማዎች ግዥ ግልፅ ጨረታ ቁጥር ቤዴ/04/2016 


የላፕቶፕ/ዶኩመንት መያዣ ቦርሳ ግዥ ገልፅ ጨረታ ቁጥር ቤዴ /05/2016

ተ.ቁ

የዕቃው ዓይነት

መለኪያ

ተፈላጊው መጠን

የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በሲፒኦ ወይንም ቅድመ ሁኔታ ባላስቀመጠ የባነክ ዋስትና (ብር)

1

የላፕቶፕ/ዶኩመንት መያዣ ቦርሳ 

በቁጥር

15,000

60,000.00

 በጨረታው ለመካፈል የሚፈልጉ ሁሉ፤

  1. የታደሰ ንግደ ፈቃዳቸውን፣ በመንግስት ግዢና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ድረ-ገጽ ውስጥ የተመዘገቡበትን፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን ማስረጃ ሰርተፍኬት ፎቶ ኮፒውን በማያያዝ የማይመለስ ብረ 110/አንድ መቶ አስር/ ለእያንዳንዱ ሰነድ በስላሴ ቅርንጫፈ በመክፈል የጨረቃ ሰነዱን ከረቡዕ የካቲት 9 ቀን 2008 ዓ.ም ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት ከጠዋት 2፡00 – 6፡00 እና ከሰዓት ከ7፡00 – 10፡30 ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ህንፃ ላይ በሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዴቨሎፕመንት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 208 በመምጣት መውሰድ ይችላሉ፡፡
  2. ተጫራቶች ስለ ጨረታዎቹ መረጃ ማግኘት ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 011-1-8910፣ 011-1228654፣ 011-1-228697 ፋክስ ቁጥር 208 በመምጣት መውሰድ ይቸላሉ፡፡
  3. ተጫራቶች ለጨረታ ማስረከበሪያ /ቢድ ቦንድ/ በሲፒኦ ሰነዱ ውስጥ በተጠየቀው መልኩ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  4. የሰንደቅ ዓላማዎች ጨረታ መጋቢተ 6 ቀን 2008 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት አና የላፕቶፕ /ዶኩመንት መያዣ ቦርሳ ጨረታ መጋቢት 8 ቀን 2008 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ከላይ በተራ ቁጥር 1 በተጠቀሰው ቦታ ይዘጋል፡፡ ተጫራቶች የሰንደቅ ዓላማዎች ጨረታ እስከ መጋቢተ 6 ቀን 2008 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ እያስመዘገቡ ሰነዳቸውን በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  5. ተጫራቶች ሰነዱ ላይ በተጠቀሰው የፍላጎት መገለጫ ዝርዝር መሰረት ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  6. የሰንደቅ ዓላማዎች ጨረታ መጋቢት 6 ቀን 2008 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት እና የላፕቶፕ /ዶኩመንት መያዣ ቦርሳ ጨረታ መጋቢት 8 ቀን 2008 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ላይ ከተራ ቁጥር 1 በተጠቀሰው ቦታ ለመገኘት ፈቃደኛ በሆኑ ተጫራቶች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ፊት ይከፈታል፡፡
  7. ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

 

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ