Catagory Lists
Tenders
Type: Construction
Organization: ጤና ቢሮ
Dead Line: 2016-05-20
Tender Detail:
የደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መንግስት ጤና ቢሮ በቤቶች ማጂ ዞን፤በከፋና በደቡብ ኦሞ ዞኖች ውስጥ 12 ጤና ጣቢያዎች ግንባታ ስራ ፤ለማከናወን ህጋዊ ተጫራቾችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡
በዚህ መሠረት፡-
- ደረጃው gc-7/bc-6 እና ከዚያ በላይ የሆኑ
- ፈቃዳቸውን እና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ምዝገባ ሰርተፊኬታቸውን ለ2008 ዓ.ም ያሳደሱ፤ ለተጨማሪ ታክስ መለያ ቁጥር ያላቸው፤
- ተጫራቾች ለሥራው የተዘጋጀውን ሠነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ30 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ዝውትር በስራ ቀናት በጤና ቢሮ ግዥ ንብ/አስ/ክፍል ቀርበው መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የብር 80,000/ሰማኒያ ሺ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም የባንክ ዋስትንና ደብዳቤ የጨረታ ዋስትና ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዶቻቸውን ቴክኒካልና ፋይናንሻል እያንዳንዳቸው አንድ ኦርጅናል እና ሁለት ፎቶ ኮፒ ለየብቻቸው በማሸግና በአንድ ኢንቨሎፕ ውስጥ በማድረግ በሰም በማሸግ ጨረታው ከወጣበት በ31ኛው ቀን ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ከጠዋቱ 3፡00-6፡00 ሰዓት ማስገባት አለባቸው፡፡
- ጨረታው በዚሁ እለት ከቀኑ በ8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- 31ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል፡፡
- መ/ቤቱ ጨረታው በሙሉ ሆነም በከፊል የመሰረዘ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 046 220 39 45/046 220 92 09/5950/9208 ሀዋሳ
የደቡብ ብሄሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት ጤና ቢሮ