Catagory Lists
Tenders
Type: Electronics
Organization: የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ
Dead Line: 2016-02-16
Tender Detail:
የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ ማየት ለተሳናቸው envoys audio player በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ስለዚህ በዚህ ጨረታ ለመወዳደር የሚፈልጉ፡፡
- ጨረታው በሚመለከት ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያለውና የ2008 ዓ.ም የንግድ ፈቃድ ያሳደሰ
- በተጨማሪ እሴት ታክስና በአቅራቢነት የተመዘገበ፤ቲን ቁጥር ያለውና የታህሳስ 2008 ዓ.ም የቫት ዲክላሬሽን የሚያቀርብ
- የጨረታ ማስከበሪያ ብር 20,000.00 የመንግሥት ግዥ መመርያ በሚፈቅደው መሰረት ማቅረብ የሚችል፡፡
- ዝርዝር የጨረታ ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቅያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀኖች መቐለ ከሚገኘው ከትግራይ ክልል ትም/ቢሮ ህንፃ 1ኛ ፎቅ ግዥ ክፍል የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 50.00 በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፡፡
- የጨረታ አሸናፊ ውል ከፈፀመበት ቀን ጀምሮ በ60 ቀናት ውስጥ ትግራይ ክልል ትም/ቢሮ መጋዘን የሚያስረክብ መሆን አለበት፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀብ ጀምሮ በተከታታይ እስከ 15ኛው ቀን 8፡30 ሰዓት ድረስ በትግራይ ክልል ትም/ቢሮ 1ኛ ፎቅ ግዥ ክልል ቀርቦ በማስመዝገብ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ የጨረታ ዶክመንት ማስገባት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ዶክመንት ፋይናንስ ኦርጅናልና ኮፒ ለየብቻው በታሸገ ፖስታ መቅረብ አለባቸው፡፡
- ጨረታው በ15ኛው ቀን በ8፡45 ታሽጎ በ9፡00 ሰዓት ይከፈታል፡፡15ኛው ቀን በዓል ከዋለ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ቀን የመዝጊያና የመክፈቻ ቀን ይሆናል፡፡
- ቢሮው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው በከፊል ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡-0344-40-34-77/40-82-99 መጠየቅ ፡፡