Catagory Lists
Tenders
Type: Multiple Items
Organization: የኢትዩጵያ ንግድ ባንክ
Dead Line: 2016-02-24
Tender Detail:
የኢትዩጵያ ንግድ ባንክ የቢዝነስ ዴቨሎፕመንት የሥራ ሂደት ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ለማስታወቂያ አገልግሎት የሚውል ኤልኢዲ እና ለስጦታ አገልግሎት የሚውሉ የቆዳ ውጤቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ለጨረታ ቁጥር ቢዴ/02/2016
የሥራው ዓይነት |
ካቢኔት መጠን |
ብዛት |
የጨረታው ማስከበሪያ ዋስትና በሲፒኦ ወይንም ቅድመ ሁኔታ ባስቀመጠው የባንክ ዋስትና(ብር) |
ማስታወቂያዎችን በጽሁፍ ምልክት፤በድምጽ እና በቪዲዩ የተቀረጹ ምስሎችን የሚያስተላልፍ ባለሙሉ ቀለም ኤልኢዲ ዲስፕሌይ |
120 cm * 180 cm |
200 |
100,000.00 |
በጨረታው ለማካፈል የምትፈልጉ ሁሉ
- የታደሰ የንግድ ፈቃዳቸውን፤በመንግስት ግዥና አስተዳደር ኤጀንሲ ድረ-ገጽ ውስጥ የተመዘገቡበትን፤የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገበቡበትን ማስረጃ ሠርተፍኬት ማቅረብ እና የግብር ከፋይ ሰርተፍኬት ፎቶ ኮፒውን በማያያዝ ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 110/መቶ አንድ ብር/በኢትዩጵያ ንግድ ባንክ ስላሴ ቅርንጫፍ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ከረቡዕ የካቲት 2 ቀን 2008 ዓ.ም ጀምሮ ዘውትር በሥራ ሰዓት ከጠዋቱ 2፡00-6፡00 ሰዓት እና ከ7፡00-10፡30 ሰዓት ቅደስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ህንፃ ላይ በሚገኘው የኢትዩጵያ ንግድ ባንክ ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 208 በመምጣት መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ስለ ጨረታው መረጃ ማግኘት ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 011-122-89-66 መጠየቅ ይችላሉ፡፡
- ለጨረታ ቁጥር ቢዴ/02/2016 ጨረታ የካቲት 17 ቀን 2008 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ከላይ ከተራ ቁጥር 1 በተጠቀሰው ቦታ ይዘጋል ፡፡ተጫራቾች እስከ የካቲት 17 ቀን 200 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ እያስመዘገቡ የጨረታ ሰነዳቸውን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ለጨረታ ቁጥር ቢዴ/02/2016 ጨረታ የካቲት 17 ቀን 2008 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ከላይ ከተራ ቁጥር 1 በተጠቀሰው ቦታ ለመገኘት ፈቃደኛ በሆኑ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ፊት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ሰነድ ላይ በተጠቀሰው የፍላገት መግለጫ ዝርዝር መሰረት ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡