Tenders

 

Type: Construction

 

Organization: የባምባሴ ወረዳ አቅ/ግን/ትም/ጽ/ቤት የአፋ-ፌርበርናሬ እና የኢዳ-ዳቡስ ቀበሌ የትምህርት ቤት

Dead Line: 2016-10-28

 

Tender Detail:

 





የባምባሴ ወረዳ አቅ/ግን/ትም/ጽ/ቤት የአፋ-ፌርበርናሬ እና የኢዳ-ዳቡስ ቀበሌ የትምህርት ቤት ሙሉ ግንባታ ተጫራቾችን አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡

የጨረታው መስፈርቶች፡-

  1. የሥራ ፈቃዳቸው ደረጃ G/C ወይም B/C 7 እና ከዚያ በላይ የሆኑ፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉና የስራ ፈቃዳቸውን ያደሱ፣ እንዲሁም በክልሉ የሙያ ብቃት ምዘና ለመውሰድ የተመዘገቡበትን ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ ተቋራጮች መወዳደር ይችላሉ፡፡
  2. ተቋራጮች የጨረታው ሰነድ ይን ማስታወቂያ ከወጣበትን ቀን ጀምሮ ለ21 ተከታታይ የስራ ቀናት ድረስ ዘወትር በስራ ሰዓት ከባምባሲ ወረዳ ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት በግንባር በመቅረብ የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
  3. ተጫራቾች የሰነዱን 1 ኦሪጅናል እና 2 ኮፒ ለየብቻው በሰም በታሸግ ኢንቨሎፕና 3ቱንም በ1 በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  4. ተጫራቾች የጨረታውን ማስከበሪያ ቦንድ CPO ወይም ህጋዊ መድን ዋስትና የተረጋገጠ 2% ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. ተጫራቾች ያላቸውን የሰው ኃይል ወይም ባሙያዎቻቸውን በክልሉ የብቃት ምዘና ምዝገባ ያደረጉ/ያላቸው ፋይናንስ ካፒታል /ገንዘብ ማሽነሪና ሊብሬአቸውን (Company profile) ማስረጃዎቻቸውን ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡   
  6. ተጨማሪ ማስረጃ ካስፈለገ ከጽ/ቤቱ ማግኘት ይቻላል፡፡
  7. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበተ በ22ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ታሽጎ ከረፋዱ 4፡30 ሰዓት ላይ በባምባሲ ወረዳ ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 03 ይከፈታል፡፡
  8. በጨረታው ለተሸነፉ ተጫራቾች የጨረታ ውጤት እንደተገለጸ ለጨረታው ዋስትና ያስያዙት ገንዘብ ተመላሽ ይደረጋል፡፡
  9. በክልሉ የተደራጁ የሙያ ማህበራት ለዚሁ ስራ ብቻ ካደራጃቸው መ/ቤት የተጻፈ የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

መረጃ ለማግኘት በስልክ ቁጥር 0917422582/0917171470 ደውለው ማግኘት ይችላሉ፡፡

ማሳሰቢያ፡- የጨረታ መክፈቻ ቀን የበዓል ቀናት እንዲሁም ቅዳሜና እሁድ ከዋለ በቀጣይ የስራ ቀን ላይ በተባለው ሰዓት ይከፈታል፡፡

የቤ/ጉ/ክ/መ/አሶ/ዞን/ባምባሲ ወረዳ ገን/ኢ/ል/ጽ/ቤት