Catagory Lists
Tenders
Type: Laboratory Equipments & Chemic
Organization: የባቱ ከተማ የመጠጥ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት
Dead Line: 2016-10-21
Tender Detail:
ድርጅታችን ለከተማው መጠጥ ውሃ አገልግሎት የሚውሉ፡-
1. የውሃ ማጣሪያ ኬሚካሎች
1.1 አልሙኒየም ሰልፌት
1.2 ክሎሪን (ፓውደር)
በመሆኑም ከታች የተጠቀሱት መስፈርቶችን የሚያሟሉ ድርጅቶችን በጨረታው እንዲሳተፉ ይጋብዛል፡፡
- በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና የሚፈለግባቸውን የዘመኑን ግብር አጠናቀው የከፈሉ ከፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢነት ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ ቀናት የባቱ ከተማ የመጠጥ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የግዥና ፋይናንስ አስተዳደር የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 5 በመገኘት የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል የጨረታውን ሰነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 5,000.00 (አምስት ሺህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ ቼክ (ሲፒኦ) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች እያንዳንዱን እቃ የሚሸጡበትን ዋጋና ጠቅላላውን ዋጋ በመግለጽ በሰም በታሸገ ፖስታ በማድረግ ሙሉ አድራሻና የጨረታውን ዓይነት በመጥቀስ ባቱ ከተማ የመጠጥ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የተጠቀሱትን እቃዎች በሙሉ ወይም በከፊል መጫረት ይችላሉ፡፡
- የጨረታውን ሰነድ ማቅረቢያ የመጨረሻ ቀን ጥቅምት 11 ቀን 2009 ዓ.ም ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት ድረስ ነው፡፡
- ጨረታው የሚከፈተው በእለቱ ጥቅምት 11 ቀን 2009 ዓ.ም ከረፋዱ በ5፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ ቢሮ ውስጥ ይሆናል፡፡
- አሸናፊዎች ያሸነፉበትን እቃ እስከ ድርጅቱ ድረስ በማቅረብ እቃው ትክክለኛነቱ በባለሙያ ሲረጋገጥ ክፍያ የሚከፈለው መሆኑን የሚስማማ መሆን አለበት፡፡
- ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 046 441 2497/046 441 2094 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የባቱ ከተማ የመጠጥ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት