Tenders

 

Type: Autos

 

Organization: ንብ ኢንሹራንስ አክሲዮን ማህበር

Dead Line: 2017-02-10

 

Tender Detail:

 

 




ንብ ኢንሹራንስ ኩባንያ አክሲዮን ማህበር ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችና የካሣ ክፍያ ፈጽሞ የተረከባቸውን ተሽከርካሪዎች፣ የተሽከርካሪ አካላትና ሌሎች ቁሳቁሶች ባሉበት ሁኔታ በጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል።  

 ተሽከርካሪዎች፣የተሽከርካሪ አካላትና ሌሎች ቁሳቁሶች መግዛት የሚፈልጉ ሁሉ በቆርኪ ፋብሪካ ወደ ሚድሮክ ተርሚናል በኩል በሚያልፈው አዲሱ አስፋልት መንገድ ገብቶ አልሙኒየም ፋብሪካ ፊት ለፊት በስተቀኝ በኩል በሚገኘው የኩባንያችን አዲሱ የተሽከርካሪዎች መቆሚያ ግቢ እና ቃሊቲ ቆርኪ ፋብሪካ ጀርባ በሚገኘው የኩባንያችን ሪከቨሪዎች በመገኘትና በማየት የሚገዙበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ እስከ አርብ የካቲት 03 ቀን 2009 ዓ.ም. ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ድረስ ደንበል ህንፃ 2ኛ ፎቅ በሚገኘው የካሣ መምሪያ ለዚሁ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ገቢ በማድረግ መጫረት ይችላሉ።  

 ጨረታው ቅዳሜ የካቲት 04 ቀን 2009 ዓ.ም. ከቀኑ 4፡00 ሰዓት በኩባንያው ዋና መስሪያ ቤት ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት ይከፈታል።  

 ሌሎች ተጫራቾች ባቀረቡት ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት የተከለከለ ነው።  

 ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ተሽከርካሪ የመነሻ ዋጋውን 10% (አስር በመቶ) በባንክ ክፍያ ማዘዣ (CPO) ማስያዝ ይኖርባቸዋል። የጨረታ መነሻ ዋጋቸው ከብር 15,000.00 (አስራ አምስት ሺህ ብር) በታች ለሆኑ ንብረቶች የጨረታ መነሻ ዋጋቸው በሚከተለው ዝርዝር መሰረት እንዲሆን ወስኗል።

የጨረታ መነሻ ዋጋ ማስያዣ

ከብር 1,000.00 በታች ............................................................ ብር 200.00

ከብር 1,001-2,000.00............................................................ ብር 500.00

ከብር 2,001.00-4,000.00....................................................... ብር 800.00

ከብር 4,001.00-14,999.00..................................................... ብር 1,000.00  

ከቀረጥ ነፃ ከሆኑት ተሽከርካሪዎች በስተቀር በሌሎች ተሽከርካሪዎች ከጨረታው በፊት ዕዳዎች ቢኖሩ በኩባንያው ይሸፈናል። በጨረታው ለተካተቱ ንብረቶች ከጨረታው በኋላ ያሉትን ማናቸውም ወጪዎች ገዥው ሙሉ በሙሉ ይሸፍናል።  

የጨረታ አሸናፊዎች ያሸነፉበት ዋጋ ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) 15% (አስራ አምስት በመቶ) በተጨማሪነት ይከፍላሉ።   አሸናፊዎች የጨረታው ውጤት ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ እስከ ቅዳሜ የካቲት 11 ቀን 2009 ዓ.ም. እስከ 6፡00 ሰዓት ድረስ ክፍያ ፈጽመው ንብረቶቹን ካልተረከቡ የጨረታው ውጤት የሚሰረዝ ሆኖ ከላይ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ገንዘብ ለኩባንያው ገቢ ይደረጋል።  

ኩባንያው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ማስታወሻ፡- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0911-784339 ይደውሉ ንብ ኢንሹራንስ ኩባንያ (አ.ማ.)